Skip to main content

የቢሮው ኃላፊ አቶ ዳዊት ሀይሉ በተገኙበት የችግኝ ተከላ መረሀ-ግብር ተካሄደ

በመትከል ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል በመካሄድ ላይ በሚገኘው የችግኝ ተከላ መርሃ- ግብር የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ መስኖና ማዕድን ኢነርጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ሀይሉ በተገኙበት በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ አምበሊ ቀበሌ የችግኝ ተከላ ተካሄዷል ።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ስኬታማና ውጤታማ እንዲሆን የተተኩሉ ችግኞች በባለቤትነት መንከባከብና መጠበቅ እንደሚገባ የቢሮው ኃላፊ አቶ ዳዊት ሀይሉ ተናግረዋል ።

ዘርፉ ለወጣቱ የስራ ዕድል ለመፍጠር ፣ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ፣ የአየር ንብረት መዛባት ለመከላከልና የውሀ ምንጮች እንዳይደርቁ ሚናው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል ።

በመርሃ ግብሩ ከክልል፣ ከዞንና ከወረዳ የተወጣጡ የተለያዩ ማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል ።

Image