Skip to main content

የቢሮ ሃላፊ አቶ ዳዊት ሀይሉ በሃዲያና ሀላባ ዞኖች በግንባታ ላይ የሚገኙ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ተመለከቱ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ውሀ ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ዳዊት ሀይሉ በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ፣ በሃላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በ1ኛ ጤፎ ቀበሌ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙትን  የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የመስክ ምልከታ አድርገዋል ።

የመስክ ምልከታውን ተከትሎ የፕሮጀክቶቹ ኮንትራክተሮች ፣ ከአማካሪ መሀንዲስና ሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በቀሪ ስራዎችና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል ።

ቀሪ ስራዎቹን በፍጥነት በማጠናቀቅ ለምርቃት ዝግጁ እንዲሆኑ የቢሮ ሃላፊው አቶ ዳዊት አሳስበዋል።

በምልከታው ከፌደራል፣ ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል ።

Image