በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ የሳዳማ-ማሱዳ ቀበሌ የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ተመረቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደረገ ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ ሳዳማ ማሱዳ ቀበሌ የንፁህ መጠጥ ውኃ ግንባታ ተጠናቆ መመረቁንና ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት መስጠት መጀመር ችሏል ።
ካቶሊክ ሪሊፍ ሰርቪስ በተባለ የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ገንዘብ ድጋፍ ፣ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የሆሳዕና ሀገረ ስብከት አስተባባሪነት ፣ በክልሉ ፣ በዞኑና በወረዳው ቅንጅታዊ እንቅስቃሴ ተገንብቶ የተጠናቀቀው የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ተጠናቆ የቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ኃይሉ እና የሚመለከታቸው የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
የውሀ ፕሮጀክቶቱ ከ19 ኪሎ ሜትር በላይ የውሀ መስመር ዝርጋታ ተደርጎ በ18 የዉሀ ቦኖዎች ተደራሽ መሆኑንና ከ15 ሺ በላይ ለሚሆኑ የህብረተሰብ አካላት አግልግሎቶት እንደሚሰጥ በምረቃው ወቅት ተገልፆአል ።
የውሀ ፕሮጀክቱን ሰርቶ ለማጠናቀቅ - $482,000 ዶላር ፈጅቷል ።
የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቱ በመጠናቀቁ ከዚህ ቀደም ለውኃ ወለድ በሽታ ተጋላጭ የነበሩ ነዋሪዎችን ጤና ከመጠበቅ ባሻገር ፣ ለንፁህ መጠጥ ውሀ ፍለጋ ይባክን የነበረ ጊዜ በመቆጠብ ለህፃናት፣ ለወጣቶችና እናቶች የተረጋጋ ማህበራዊ ክዋኔ ተሳትፎ የሚያጎለብት መሆኑን አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል ።
Wolkite , Ethiopia
cerswimb10@gmail.com
+251113658301 