በላይኛው ብላቴ ተፋሰስ አካባቢ ለሚካሄድ የከርሰ ምድር ሀብት አለኝታ ልየታ ጥናት ጉድጓድ ውኃ ቁፋሮ የሚውል ዘጠኝ ቦታዎች/site ርክክብ መካሄዱን ቢሮው አስታወቀ ።
ታህሳስ 09/2018 (ወልቂጤ)
በውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር እየተተገበረ የሚገኘው የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል የሆነው በላይኛው ብላቴ ተፋሰስ አካባቢ ለሚያካሄደው የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት አለኝታ ልየታ ጥናት ጉድጓድ ቁፋሮ የሚውል በክልሉ በሚገኙ አራት ዞኖች ውስጥ ዘጠኝ ቦታዎች / site ለአሸናፊ ተቋራጮችም ማስረከብ መቻሉን በቢሮ ኅላፊ ማዕረግ የክልሉ ውሀ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ምክትልና የውሀ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ አለይካ ሽኩር ገልፀዋል ።
በዛሬው ዕለት በከምባታ ዞን በአንገጫ እና አዴሎ ወረዳዎች ሀለት ቦታዎችን/Site ሀይድሮ ኢንጂነሪንግ ድርጅት እንዲረከብ መደረጉን ተናግረዋል ።
የቁፋሮው አላማው ከአገልግሎቱ ባሻገር የከርሰ ምድር ውሃ አለኝታ /potential በአቅም በጥረት ማወቅና ለቀጣይ ጥናት በተደረጉ አካባቢዎች ላይ የውሀ ጉድጓድ ቁፋሮ ቦታዎችን ዲዛይን ለማድረግ መሆኑን ወ/ሮ አለይካ ገልፀዋል ።
በቦታ ርክክቡ ላይ የተገኙት የከምባታ ዞን ውሀ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ አብነት ወትሮ በበኩላቸው የቁፋሮ ስራው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ እንዲሁም የውሀ ግኝቱን ተከትሎ ለሚከናወኑ ተግባራት መምሪያውም ሆነ የሚመለከታቸው የክልል እና ዝአካላት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል ።
በርክክቡ ወቅት ከፎደራል ሲኒየር ሀይድሮጂኦሎሲስት አቶ ገለቲ በላይ፣ የክልል ፣ የዞንና የየወረዳዎቹ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል ።
የቢሮ ኃላፊ መልዕክት
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ኃላፊ መልዕክት
አቶ ዳዊት ሃይሉ ገሮ
ኢትዮጵያ አገራችን በተለያዩ ወንዞች፣ ጅረቶች፣ ሐይቆች እና የውሀ አካላት የታደለች እና በተፈጥሮ ፀጋ የተቸረች ሀገር ከመሆኗም በላይ በአስራ ሁለት ትላልቅ የውሀ ተፋሰሶች የተከፈለች አገር ናት፡፡ ምንም እንኳን የተለያዩ ወንዞችና ሐይቆች ባለቤት ብንሆንም የውሀ ሀብቶቻችንን እንደ ሀገር ሙሉ በሙሉ በተገቢው መንገድ መጠቀም አለመቻላችን በውስጣችን ቁጭት እንዲፈጠር አድርጓል፡፡ ከዚህ አንፃር የውሀ ሀብቶቻችንን እና የተፈጥሮ ፀጋዎቻችንን በአግባቡ በማልማት፣ በማበልፀግና ለዜጎቻችን ምቹና ተስማሚ በማድረግ ጥቅም ላይ ለማዋል የውሀ ሀብቶቻችንን የማልማት፣ የማስተዳደር፣ የመንከባከብ እና በተገበው መንገድ ለመገልገል በመንግስት ረገድ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሰጥ ከላይ ከተገለጹት እንደ አገር ካሉን አስራ ሁለት ተፋሰሶች መካከል ሁለት ትላልቅ የኦሞ ጊቤ እና የስምጥ ሸለቆ ተፋሰሶች በክልላችን በሚገኙ አካባቢዎች የሚያቋርጡና በርካታ የክልልን ክፍሎች ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተፋሰሶች ናቸው፡፡ እነዚህ ተፋሰሶች በርካታ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢከኖሚያዊ ጥቅሞች ለክልሉ ማህበረሰብ የሚሰጡ ናቸው፡፡ እንደሚታወቀው የግልገል ግቢ ሁለት የውሀ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ የተመሰረተና በየም ዞን ውስጥ የሚገኝ የተፋሰሱ ትልቁ ቱሩፋትና ልዩ ትኩረት የሚፈልግ አካባቢ ነው ተጨማሪ ያንብቡ
የቢሮው አመራሮች
|
|
|
|
|
|
|
|
Wolkite , Ethiopia
cerswimb10@gmail.com
+251113658301 



































